11/04/2026
በተደደጋሚ አሰከፊ የትራፊክ አደጋ ለሚከሰትበት ለበዴሳ ከተማ አከባቢ ዘላቂና ፍቱን መፍትሔ ለከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎች የሚሆን (Bypass highway) መገንባት ያስፈልጋል።
==========================
በበዴሳ ከተማ ውስጥ ከወላይታ ሶዶ ወደ ሐዋሳ በሚዘልቀው የአገር አቋራጭ መንገድ ከማዮ ቆቴ እስከ በዴሳ ወንዝ ድረስ ወደ 15 ኪሎ ሜትር የሚሆነው ከፍተኛ ቁልቁለት በመሆኑ እና የአስፋልት መንገዱ ሲሠራ የመንገድ ደህንነት እርምጃዎች አስቀድሞ በሳይንሳዊ ጥናት መሠረት ባለመወሰዱ በተደጋጋሚ የሰው ሕይወት እየቀጠፈ፣ ከፍተኛ የንብረት መውደም እያስከተለ እና ዜጎችን ለከፍተኛ የስነልቦና ጫና እያዳረገ ይገኛል።
ችግሩን ለመፍታት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ሻሸመኔ ዲስትሪክት የተወሰኑ የመፍትሔ እርምጃዎችን ለአብነት፦ የፍጥነት መቀነሻ/speed break) በተወሰኑ አከባቢዎች መሥራቱ፣ የማስጠንቀቂያ ቢልቦርድ ብሰቅልም፣ የመንገድ ዳር ምልክት ብተክልም እንዲሁም የመንገድ ጎን መከላከያ ኮንክርት ግንብ በበዴሳ ወንዝ አከባቢ ቢገነባም ችግሩን በዘላቂነት መፍታት አልቻለም፤ በወቅቱ የተጀመሩ መልካም ሥራዎቹም ሳይጠናቀቁ መንገድ ላይ ቆሟል። ከማዮ ቆቴ ቀበሌ ዳልቦ ማዞሪያ እስከ በዴሳ ወንዝ ድረስ አሁንም የመንገድ ደህንነት ሥራዎች በልዩ ትኩረት ቢሠሩ መልካም ነው።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ፍቱን አማራጭ መፍትሔ ከባባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች ከፍተኛ የትራፍክ መጨናነቅ ያለበትን የከተማውን መሐል መንገድ ትቶ የከተማውን ዳር አቋርጠው የሚያልፉበት 4 ኪሎ ሜትር የሚሆን የማሳለጫ መንገድ መገንባት ነው። አሁን ከተማዋን አቋርጦ የሚያልፈው መንገድ ዲዛይን ቁልቁለታማ ቦታዎችን የሚቀንስና በባለወልድ ቤተክርስቲያን በራፍ አድርጎ የሚያልፈው የትራፊክ አደጋን የሚቀንስ ከመሆኑም በተጨማሪ የከተማዋን ዕድገት የሚያሳልጥ ነበር፤ አሁን ከተማዋን አቋርጦ የሚያልፈውም ቢሆን በአማራጭነት የሚሠራበት ዕድሎች የነበሩ ቢሆንም ምክንያታዊ ባልሆነ በእርስ በርስ ጭቅጭቅ የመከነ ዕድል ሆኗል።
ወደ በዴሳ ከተማ ከመገባቱ አስቀድሞ በቢልቦ በዴሳ፣ በባለወልድ ቤተክርስቲያን ዞሮ እስከ በዴሳ ወንዝ የሚዘልቅ ማሳለጫ መንገድ ቢገነባ በከተማው ውስጥ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅን በመቀነስ፣ የትራፊክ አደጋን በመቀነስ፣ የትራንስፖርት አገልግሎትን በማሳለጥ፣ የትራፊክና የመንገድ ደህንነትን በማሻሻል፣ የከተማውን ገጽታ በማሻሻል፣ ወዘተ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታዎችን ከማስገኘት አንጻር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል። [ከሙያዬ አንጻር የሰጠሁት የግል አስተያየቴ እንደሆነ ልብ በሉልኝ]
በመሆኑም የፈዴራል መንገዶች ባለሥን ERA ለዚህ መንገድ በመፍትሔ ዙሪያ ትኩረት ሰጥቶ መሥራት ይገባል፡፡
ዘውትር የዜጎቻችን ሕይወት መገበር እና የልብ ስብራት በቃ ልባል ይገባል።